የብሪጅ ዳሰሳዊ ምልከታ፦ የኢትዮጵያ ሴቶች የእንደራሴነት መንገድ፣ ከማርች ስምንት ማዶ

ወሩ መጋቢት እንደመሆኑ፣ ኢትዮጵያም 50ኛውን የሴቶች ቀን ደርበብ ባለ ሥርዓት አስባው ውላለች። ሴት እንደራሴዎቹም በ‘የዓመቱ መጋቢት 4 ቀን የሚከበረውን ይኽንኑ ዓለም ዓቀፉን የሴቶች ቀን አክብረው ውለዋል። የእንደራሴዎቹ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ዓለም ዓቀፉ የሴቶች ቀን፣ “የሴቶች ድምጽ ለእኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች መከበሩን የምክር ቤቱ ዘገባ ጠቅሷል። […]
የብሪጅ የሕግ ሥነ-ሐሳብ ዳሰሳዊ ምልከታ፦አዲሱ የኢትዮጵያ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ ለውጦች እና ሙግቶች፣

የኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት ለ65 ዓመታት ያህል ሲመራበት የቆየውን እና በ1954 ዓ.ም. በንጉሠ ነገሥቱ ዘመን የጸደቀውን የሥነ-ሥርዓት ሕግ በመሻር፣ አዲስ ምዕራፍ ተቀላቅሏል። የማርቀቅ ሂደቱ ዐሥራ አምስት ዓመታት በላይ የፈጀው ይኽ ታሪካዊ ሰነድ፣ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው 13ኛው የኢፌድሪ የእንደራሴዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር […]
የብሪጅ ዳሰሳዊ ምልከታ፦ በአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እና ተያያዥ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ

ኢትዮጵያውያን በብዙ ተስፋም፣ በከፊል ጥርጣሬም እየተመለከቱት ያለው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በተለያዩ ድርብርብ ምክንያቶች የተነሳ ባቀደው ልክ መጓዝ አለመቻሉ በወርኃ የካቲት አጋማሽ ላይ ተሰምቷል። ይኽን ግንዛቤ ውስጥ የከተተው የኢትዮጵያ እንደራሴዎች ምክር ቤትም፣ የኮሚሽኑን ተግዳሮቶች አሳማኝ ሆነው ስላገኛቸውም የተቋሙን ዕድሜ በስምንት ወራት አራዝሟል። ምክር ቤቱ ለ8 ወራት እንዲራዘም የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ አጸድቆታል። የእንደራሴዎቹ ምክር […]