BRIDGE Research & Innovation - Parliaments. Peace. Policy

የሐረሪ ሕዝብ ክልል የተሻሻለዉ ሕገ መንግስት (1997)

ክልሉ /ቤት አወቃቀርና፣ አወካከል፤ ሥልጣንና ተግባር

አንቀጽ 48

የሐረሪ ህዝብ ክልል ምክር ቤት

የሐረሪ ሕዝብ ክልል ም/ቤት 36 አባላት ያሉትና በሁለት ጉባኤዎች የተወቀረ የክልል ም/ቤት ነው፡፡

አንቀጽ 49

የም/ቤቱ ጉባኤዎች

  1. የሐረሪ ሕዝብ ክልል ም/ቤት ሁለት ጉባኤዎች፡-

ሀ/ የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤና

ለ/ የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ናቸው

  1. የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤበዚህ ህገ መንግስት አንቀጽ 50/1/1 እንደመለከተው የሚወከሉ 14 የሐረሪ በሔረሰብ አባላት ይኖሩታል፡፡
  2. የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ በዚህ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 50/2/ እንደተመለከተው የሚወከሉ 14 የሐረሪ በሔረሰብ አባላት ይኖርታል

አንቀጽ 50

የጉባኤዎች አከፋፈል አወካከልና አመራረጥ

  1. የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤ አባላት በሁለት የምርጫ ክልሎች የሚወከሉ አባላት ያሉት ጉባኤ ነው፡፡

አወካከሉ፡-

ሀ/ ከጆገል ምርጫ ክልል 4 አባላትና

ለ ከጆገል ውጭ ካሉት የከተማ ቀበሌዎችና የገጠር ቀበሌ ገበሬ ማህበራትን የሚያጠቃልል  የምርጫ ክልል 18 አባላት ይመረጣል፡፡

  1. የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አባላት በክልሉ ውስጥና ከክልሉ ውጭ በሌላ በኢትዮጽያ ከልሎችና ከተሞች ከሚኖሩ የሐረሪ ብሔረሰብ አባላት ይመረጣል፡፡
  2. የጉባኤው አባለት ምርጫ ነፃና ቀጥተኛ በሆነ ድምጽ በሚስጥር በመስጠት ስርዓት ይፍጽማል

ክፍል አንድ

ስለ ክልሉ ምክር ቤት

አንቀጽ 51

የሐረሪ ሕዝብ ክልል /ቤት ሥልጣንና ተግባር

  1. የሐረሪ ሕዝብ ክልል ም/ቤት የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤና የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ በጋራ የሚሰበሰቡበት ም/ቤት ነው፡፡ በዚህ ህገ መንግስት መሠረት የክልሉ ህግ አውጪና በክልሉ የውስጥ ጉዳዮች ላይ የበላይ የፖለቲካ ስልጣን ባለቤት ነው፡፡
  2. የሐረሪ ሕዝብ ክልል /ቤት የሚተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡፡

ሀ/ የክልሉን ሕገ- መንግስትና ሌሎች ሕጎችን ያወጣል፡፡

ለ/ በዚህ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 79 በተደነገገው መሠረት የክልሉን ሕገ- መንግስት ያሻሽላል፡፡

ሐ/ የፌደራል ሕገ- መንግስት ለክልሎች የተሰውን ስልጣን በክልሉ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡

መ/ ለክልሉ ኘሬዚዳንት በሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ ጠቋሚት የሚቀርበውን እጩ በ2/3ኛ ድምጽ መርምርሮ ይመርጣል፡፡

ሠ/ የክልሉን የውስጥ አስተዳደር ያዋቅራል ያደራጃል፡፡

ረ/ የክልሉን የሕዝብ ደህንነትና ፀጥታን በሚመለከት ሕጎች ደንቦችና መመሪያዎት ያወጣል

ሰ/ የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤና በክልሉ መስተዳደር ም/ቤት የሚቀርቡለትን አዋጆች ደንቦች መመሪያዎችና ፖሊሲዎች መርምሮ ይፀድቃል፡፡

ሸ/ በክልሉ ኘሬዚዳንት የቀረቡትን ም/ኘሬዚዳንት የክልል አስፈፃሚ/ካብኔ/ አባል የሆኑ የቢሮ ኃላፊዎትና ሌሎች ተመሳሳይ ስልጣን ያላቸውንና ኃላፊዎች ሹመት ያፀድቃል፡፡

ቀ/ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ኘሬዚዳንት ምክትል ኘሬዚዳንትና ዋና ኦዲተር እና የፖሊስ ኮምሽነር ይሾማል።

በ/ በክልሉ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የሚቀርቡበትን ዳሄት ሹመት ያፀድቃል፡፡

ተ/ የክልሉን የመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ፣ ደንብና መመሪያ የወጣል፡፡

ቸ/ ለክልሉ በተሰጠው የገቢ ምንጭ ወሰን ግብርና ታክስ ይጥላል፡፡

ነ /የክልሉን አመታዊ በጀት ይፀድቃል፡፡

ኘ/ በክልሉ ውስጥ ማናቸውም ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ ሲየጋጥም ወይምየሕዝብን ጤንነት አደጋ ላይ የሚጥጭ በሸታ ሲከሰት የአስቸኩይ ጊዜ አዋጅ ያውጃል፡፡

አ/ የክልሉን መንግስት የገቢ ምንጮች የሚመለከቱ ሀጎች ያወጣል፡፡

ወ/ በህጉ መሰረት ምህረት ያደርጋል፣ የክልሉን ሠላምና ፀጥታ ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ መመሪዎችን ያወጣል፡፡ የፀጥታና የፖሊሲ ሃይሉን ያቋቁማል

የ/ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ሌሎች የክልሉን መንግስት ባለስልጣናት ለጥየቄ ይጠራል የአስፈፃሚዉን አካል አሠራር ይመረምራል፡፡

አንቀጽ 52

የም/ቤቱ አመራርና አሠራር

  1. ም/ቤቱ የራሱ አፈ ጉባኤና ምክትል አፈ-ጉባኤ ይኖሩታል፡፡
  2. እንደአስፈላጊነቱ ቋሚና ጊዜያዊ ኮሚቴዎች ይኖሩታል፡፡
  3. አፈ-ጉባኤው በዝብ ተወዮች ጉባኤ በኩል እንዲሁም ምክትል አፈ-ጉባኤ በኩል እንዲሁም ምክትል አፈ-ጉባኤ በሐረነ በሔራዊ ጉባኤ በኩል ቀርበው በምክር ቤቱ በ2/3ኛ ድምጽ ይምረጣሉ፡፡

አንቀጽ 53

የአፈጉባፌው ስልጣንና ተግባር

1.የም/ቤቱን መደበኛና አስቸኳይ ስብሰባዎች ይጠራል፡፡ ይመራል፡፡

  1. የም/ቤቱን ጠቅላላ ሥራዎች ያስተዳድራል፡፡
  2. በም/ቤቱ አባላት ላይ የሚወሰኑ የዲሲፒሊን እርምጃዎችን ያስፈጽማል፡፡
  3. የአፈ-ጉባኤው ሌሎች ሥራዎች በዝርዝር የሚወጣ ሌላ ሕግ ይወሰናል፡፡

አንቀጽ 54

የምክትል አፈጉባኤው ስልጣንና ተግባር

  1. በአፈ -ጉባኤ ተለይቶ የሚሰጡትን ተግባራት ያከናውናል፡፡
  2. አፈ-ጉባኤው በማይኖርበት ጊዜ ተክቶ ይሰራል፡፡

አንቀጽ 55

የም/ቤቱ አባላት መብትና ግዴታ

  1. ማንኛውም የም/ቤቱ አባል በም/ቤቱ በሚሰጠው ድምጽ ወይም አስተያየት ምክንያት አይከሰስም አስተዳደራዊ እርምጃ አይወሰድበትም፡፡
  2. ማንኛውም የም/ቤቱ አባል ከባድ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፈንጅ ካልተያዘ በስተቀር ያለ ም/ቤቱ ፈቃድ አይያዝም በወንጀልም አይከሰስም፡፡
  3. ማንኛውም የም/ቤቱ አባል የመረጠው ሕዝብ አመኔታ በጣበት ጊዜ ከም/ቤት አባልነት ይወገዳል፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይዋሰናል፡፡

አንቀጽ 56

የም/ቤቱ የስብሰባ ጊዜና የሥራ ዘመን

  1. ም/ቤቱ በዓመት ሁለት ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል፡፡
  2. የም/ቤቱ አባላት የሥራ ዘመን ለአምስት አመት ነወ፡፡ የስራ ዘመኑ ከማብቃቱ ከአንድ ወር በፈት አዲስ ምርጫ ተካሄዶ ይጠናቀቃል፡፡ የቀድሞው ም/ቤት የሥራ ዘመን በተጠናቀቀ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ አዲሱ ም/ቤት ሥራውን ይጀምራል፡፡
  3. የም/ቤቱ መደበኛ ስብሰባ በማይኖርበት ወቀት አፈ-ጉባኤው አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይም ከምክር ቤት አባላት መካከል ከ1/3ኛ በላይ የሚሆኑት አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠሩ ከጠየቁ አፈ-ጉባኤው ስብሰባ እንዲጠሩ ከጠየቁ አፈ-ጉባኤው ስብሰባ የመጥራት ግዴታ አለበት፡፡
  4. የም/ቤቱ ስብሰባ በግልጽ ይካሄዳል፡፡ ሆኖም ስብሰባው በዝግ እንዲካናድ በአባላቱ ወይም በክልሉ መስተዳደር ም/ቤት ከተጠየቀና ከም/ቤት አባላት መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ጥያቄውን ከደገፉት ዝግ ስብሰባ ሊደረግ ይችላል፡፡

አንቀጽ 57

የውሳኔ  አሰጣጥና የአሰራር ሥነሥርዓቶች

  1. ከም/ቤት አባላት መካከል ከ2/3ኛ የሚሆኑት ከተገኙ ምልዓተ ጉባኤ ይሆናል፡፡
  2. ማንኛውም ውሳኔ የሚተለለፈው በም/ቤቱ ስብሰባ ላይ በተገኙት አባላት አብላጫ ድምጽ ይሆናል።
  3. ምክር ቤቱ አሰራሩንና የሕግ አወጣጥ ሂደቱን አስመልክቶ ዝርዝር ሕጎችን ሊያወጣ ይችላል፡፡

ክፍል ሁለት

የጉባኤዎች ስልጣንና ተግባር

አንቀጽ 58

የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤ ስልጣንና ተግባር

የሕዝብ ተወካዮች ጉባኤ በክልል ም/ቤት ከሚኖረው ስልጣንና ተግባር በተጨማሪ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባር በተጨማሪ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡፡

  1. ማንኛውም የኢኮኖሚ ልማትና የማህበራዊ ልማት ፖሊሲ ስትራቴጁ በተመለከተ ረቂቅ ሕግ ያመነጫል፣ ለክልሊ ም/ቤት አቅርቦ ይፀድቃል፡፡
  2. የግብርና ታክስ አዋጆችን ያመነጫል፣ ለክልሊ ም/ቤት በማቅረብ ያፀድቃል፡፡
  3. የክልሉን በጀት ገምግሞ ለክልሊ ም/ቤት ያቀርባል፤
  4. በክልሉ የም/ቤት አባላት መካከል አፈ-ጉባፌነት አንድ አባል ይጠቁማል፡፡
  5. የጉባኤውን ስብሰባ የሚመሩ አፈ-ጉባኤ፣ምክትል ጉባኤና
  6. የጉባኤው ቃለ ጉባኤ የሚይዝ አንድ ፀሐፊ ይመርጣል፡፡
  7. የራስን እድል በራስ የመወሰን መብትን በዚህ ህገ መንግስት አንቀጽ 39 መሰረት ተግባራዊ ያደርጋል።