ወርኃዊ ጥንቅር ቁ.001 መጋቢት 2017 ዓ.ም

ይኽ ቀዳሚው የመጋቢት ወር የእንደራሴ ዕትም፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ እንደራሴዎች ካከናወኗቸው አበይት ተግባራት መካከል፣ የምክር ቤቱ ተልዕኮዎች የሆኑትን አራት ዋንኛ ጉዳዮችን አካቷል። እነዚህም፣ ሕግ ማውጣት፣ የተመራጭነት ውክልና፣ የአሥፈጻሚ አካላት ቁጥጥር እና የፓርላማ ዲፕሎማሲ ናቸው። ከአሥፈጻሚ አካላት ቁጥጥር ተግባራት ውስጥ የሚካተተው፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትርሚ ዐቢይ አሕመድ፣ የፌዴራል መንግሥቱንት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት አፈፃፀምን መነሻ በማድረግ፣ እንደራሴዎቹ […]