ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ

ማዕከላዊ መንግሥቱ ኃይል የሚጠቀመው በምን ኹኔታ እና ምን ሲገጥመው ነው? የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ጉዳይስ? ኢኮኖሚውስ እንዴት ሰንብቷል? በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው ዙር፣ 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፣ 21ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የተገኙት የአገሪቷ ርዕሰመንግሥት፣ ይኽን መሰሎቹን ጥያቄዎች ጨምሮ፣ በዛ ባሉ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ምላሾችን ሰጥተዋል፤ አኹናዊ የመንግሥታቸውን አቋሞችም አስረድተዋል። ኢኮኖሚው እንዴት ሰነበተ?
የብሪጅ ዳሰሳዊ ምልከታ፡ የመስክ ስራዎች

የኢትዮጵያ እንደራሴዎች፣ ወደ ‘ምርጫ ወረዳዎቻቸው በመሄድ፣ ከወከሏቸው መራጮቻቸው እና በየአካባቢዎቻቸው ከሚገኙ ተቋማት ጋር በቀጥታ በመገናኘት የመስክ ጉብኝቶችን አድርገዋል። በዚኽ የመስክ ጉብኝቶቻቸውም፣ በሄዱባቸው አካባቢዎች ስለተከናወኑና በመከናወን ላይ ያሉ የልማት እንቅስቃሴዎችን እና ተግዳሮቶችን በመገምገም ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ችለዋል።
የምክር ቤቱ የውክልና ሥራ

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሚጠበቁባቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የውክልና ሥራ ነው። እንደራሴዎቹም ወደ ‘ምርጫ ወረዳዎቻቸው በመሄድ የወከሏቸውን ማወያየት እና ጥያቄዎቻቸውን መስማት፣ በዓመት ኹለት ጊዜ የሚከውኑት ተግባር ነው። ከዚኽ አኳያም፣ የምክር ቤቱ አባላት ይኽንኑ የውክልና ሥራቸውን ከየካቲት ወር በመቀጠል በመጋቢት ወርም ከውነዋል።
የምክር ቤቱ ሕግ የማውጣት ተግባሮች

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኹለት አዋጆችን ያጸደቀ ሲሆን፣ አንድ ረቂቅ አዋጅን ለሚመለከተው የቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ ልኳል፤ ከዚኽ በተጨማሪ፣ ሦሥት የአስረጂ መድረኮችን በረቂቅ ሕጎቹ ላይ አከናውኗል፡፡ የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ በወርሃ መጋቢት ካፀደቃቸው ሕግጋት አንዱ፣ የተመሠከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲቲዩት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅን ነበር።
የብሪጅ ዳሰሳዊ ምልከታ፡ በአዋጅ ቁጥር 1373/2017 ላይ የተደረገ

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል መንግሥቱ በክልሎቹ ውስጥ ጣልቃ የሚገባበትን ነባር አዋጅ አሻሽሏል። ምክር ቤቱ፣ መጋቢት 23 2017 ዓ.ም. ባካሄደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባው፣ የቀረበለትን ይኽንኑ የማሻሻያ አዋጅ ያፀደቀው በኹለት ድምጸ-ተዐቅቦ በአብላጫ ድምጽ ሲሆን፤ ነባሩን አዋጅ ቁጥር 359/1995ን ተክቶ አዋጅ ቁጥር 1373/2017 በሚል አፅድቆታል።